Thursday, July 28, 2016

የኤጲፋንዮስ ቅዳሴ



(ክፍል አንድ)      
  • እግዚአብሔር በገናንነቱ ገናና ነው፤ በቅድስናው የተቀደሰ ነው፤ በምስጋናው የተመሰገነ ነው፤ በክብሩም የከበረ ነው፡፡
  •  ከመቼ ወዲህ የማይሉት ቀዳማዊ ነው፤ እስከዛሬ የማይሉት ማእከላዊ ነው፣ እስከዚህ የማይሉትም ደኃራዊ ነው፡፡
  • ለአነዋወሩ ጥንት የለውም፤ ለአኳኋኑም ፍጻሜ የለውም፤ ለዘመኑ ቁጥር የለውም፤ ለውርዝውናውም ማርጀት የለበትም፤ ለኃይሉም ጽናት ድካም የለበትም፤ ለመልኩ ጥፋት የለበትም፡፡ ለፊቱ ብርሃንም ጨለማ የለበትም፡፡
  • ለጥበቡ ባሕር ድንበር የለውም፤ ለትእዛዙም ይቅርታ መስፈርት የለውም ለመንግሥቱ ስፋት ዐቅም ልክ የለውም፣ ለአገዛዙም ስፋት ወሰን የለውም፡፡
  • በኅሊና የማያገኙት ሥውር ነው፤ በልቡናም የማይረዱት ምጡቅ ነው፤ አንሥርት የማይደርሱበት ረጅም ነው፤ ዓሣዎች የማይዋኙበት ጥልቅ ነው፡፡
  • ከተራሮች ራስ ይልቅ ከፍ ያለ ነው፤ ከባሕር ጥልቅነት ይልቅ ጥልቅ ነው፤ ነገሥታት የማይነሳሱበት ጽኑ ነው፤ መኳንንት የማይቃወ አሸናፊ ነው፡፡
  • የጥበበኞችን ምክር የሚያጠፋ ጥበበበኛ ነው፤ የሚመክሩትን ሰዎች አሳባቸውን የሚያስረሳ ዐዋቂ ነው፤ የጸኑ ልጓሞችን የሚፈታ ኃያል ነው፤ የኃጥአንን ጥርሶች የሚያደቅ፣ የትእቢተኞችንም ክንድ የሚቀጠቅጥ ብርቱ ነው፡፡
  • የግብዞችን ፊት የሚያዋርድ ክቡር ነው፤ የዝንጉዎችን ብርሃን የሚያርቅ ከሃሊ ነው፡፡
  • ባልንጀራ የሌለው አንድ ነው፤ ዘመድ የሌለው ሥሉጥ ነው፤ ሰማ ይጠፋሉ፤ የብስም ትጠፋለች፤ ሁሉም  እንደ  ልብስ ያረጃል፡፡ እርሱ ግን እስከ ዘለዓለሙ  እርሱ ነው፡፡
  • የባሕር መመላለሷ ድንቅ ነው ድንቅስ በልዕልናው እግዚአብሔር ነው የሚመስለው የለምከፍጥረትም ሁሉ ከአማልክትም ልጆች ሁሉ የሚተካከለው የለም፡፡ እርሱ ብቻ አምላክ ነው እርሱም ብቻ ጌታ ነውፈጣሪም እርሱ ብቻ ነውሪም  እርሱ ብቻ ነው፡፡
  •  ስላሰበው ጥበብ እረዳት አይሻም ስለ ወደደውም ሥራ መካር አይሻም፡፡ ሳይሆን ቀድሞ እንደ ሆነ አድርጎያልተደረገውንም  እንደ ተደረገ አድርጎ ሁሉን ያውቃል፡፡
  • ሳይጠይቅ ሊናን ይመረምራልሳይመረምር ልቡናን ይፈትናልያለመብራት በጨለማ ያለውን ያያል፡፡
  • ጻድቁን ጽድቅን ሳይ ያውቀዋል ኃጥኡንም ኃጢ ሳይ ያውቀዋልልበኞችን ከአባታቸው ወገ(አብራክ) ሳይወጡ  ያውቃቸዋልኃጥአንንም  ከእናታቸው ጸን ያውቃቸዋል፡፡
  • የሚሸሸገው የለም የሚሰወረውም የለምርሱም  የሚሰወር የለምሁሉ ርሱ ዘንድ የተገለጸ ነውበዓይኖቹም ፊት ሁሉ የተዘረጋ ነው፡፡ ሁሉ በመጽሐፉ  የተጻፈ ነውሊናውም ሁሉ የተጠራ ነው፡፡
  • ቁጥር የሌላቸው ታላላቆችን መመርመር የሌለባቸውን የተደነቁ የከበሩ ራዎችን ራል:: ራው ካየነው  ይልቅ እጹብ ነውኃይሉም  ከሰማነው  ይልቅ ድንቅ ነው  ጌትነቱም  ከነገሩን ይልቅ ድንቅ ነው፡፡
  • ከጨለማ ለይቶ ብርሃንን ፈጠረ ደመናውን መለየት ያውቃል፡፡ ውን እንደወደደ ይከፍለዋልየተመረጡትን በደመና ውራል፡፡
  • ምድርን ፈጠራት መጠኗንም  አዘጋጀፍጻሜዋንም  እንደምንም  ተከለ ማዕዘኗንም አጸና፡፡
  • ባሕርን ከእናቷ ሆድ በወጣች ጊዜ በበሮች አጠራት፡፡ ልብሷንም ደመና አደረገላትበጉም ጠቀለላት ወሰን አደረገላትስጧም መዝጊያዎችንና ቁልፎችን አደረገላት፡፡ ‘‘እስከዚህ ድረሺከወሰንሽም  አትተላለፊ ማዕበልሽ በውስጥሽ ይመላለስ (ይነቃነቅ) እንጂ’’ አላት፡፡
  • በበላይዋ ላይ የንጋት ብርሃን ተዘጋጀየአጥቢያ ኮከብም ትእዛዙን ዐወቀ፡፡ እርሱ ከምድር ጭቃን ሕያው የሆነውን ፈጠረ፡፡ በምድርም ላይ እንዲነጋገር አደረገው፡፡
  • እርሱ እስከ ዓለም ዳርቻ ደረሰ፡፡ በጥልቅ ፍለጋም  ተመላለሰ፡፡
  • ከግርማው  የተነሳ የሞት ደጆች ይከፈታሉየሲኦል በሮችም ባዩት ጊዜ ይደነግጣሉ፡፡ ከሰማይ በታች ያለውን ስፋቱን ከሰማይ በላይ የሚሆነውንም  እርሱ ያውቀዋል፡፡
  • ርሱ ትእዛዝ ዋግ ከመዝገቡ ይወጣል፡፡ ከሰማይ በታች ያለ አዜብ (ነፋስ ) ይመላለሳል፡፡ ዝናምን በምድረበዳ ያጸናዋል ሰው በሌለበትና የሰው ልጅ በማይኖርበት ይዘንም ዘንድ፡፡
  • እርሱ የውውን መፍሰሻ ወሰነ ክረምትንም በያመቱ ይከፍታል በጋውንም በጊዜው ጊዜ ያመጣዋል፡፡ደመናውንም በቃሉ ይጠራዋል ውኃ  እየተንቀጠቀጠ  ይመልስለታል፡፡
  • ብልጭልጭታውንም እርሱ ይልከዋል እርሱም ይሄዳል ‘‘ምንድር ነው?’’ እያለ ይመልስለታል፡፡ እርሱ ደመናን በጥበቡ ይቆጥረዋል፡፡ ሰማይን (ጠፈርን ) ወደ ምድር ያዘነብለዋል፡፡
  • እርሱ ብቻ የአርያምን ኃይል ለበሰ በምስጋናና በክብር ተጌጠ፡፡
  • እሳታውያን ኪሩቤል ብርሃን የለበሱ ሱራፌልም እርሱን ያመሰግናሉ፡፡ በማያርፍ ቃል ዝም በማይል በማይደክምም አንደበት ሁሉም ተባብረው ተሰጥዎ ባለበት ባንድ ቃል ‘‘የጌትነትህ ምስጋና በሰማይ በምድር የመላ ፍጹም  አሸናፊ ቅዱስ ቅዱስ ቅዱስ እግዚአብሔር’’ ይላሉ፡፡
  • ፍጹም አሸናፊ እግዚአብሔር የጌትነትህ ምስጋና በሰማይና በምድር የመላ ነው፡፡
  • ሁሉ ርሱ ነውሁሉም  ስለርሱ ነውሁሉም  ርሱ ነውሰማይ ርሱ ነውከሰማያት በላይ ያለ ሰማይም  ርሱ ነውየአርያም ስፋት የክብሩ ዙፋን ነውየምድርም ስፋት የእግሩ መመላለሻ ናት፡፡
  • ፀሐይ ርሱ ነውጨረቃም ርሱ ነውከዋክብትም የእጁ ሥራ ናቸው ደመናት መልክተኞቹ ነፋሳትም  ረገላዎቹ ናቸውእሳትም  የቤቱ ግርግዳ ነው፡፡
  • የቤቱ ጠፈር ውኃ ነውየዙርያውም ጸፍጸፍ የበረድ ሰሌዳ ነውድንኳኖ ብርሃናት ናቸው፡፡ የመሰወሪያ መጋረጃውም  የብርሃን መብረቅ ነውመመላለሻውም በአየር ነው ::
  • የመናገሩ ድምፅ በብልጭልጭታ ያለ ነው፡፡ የነጎድጓዱ ቃል ረገላዎች አለ፡፡ ባሕር ባሪያው ናት የወንዝ ፈሳሾች ተገዥዎቹ ናቸው፡፡ ቁር አስሐትያም  ፈቃዱን የሚ ናቸው፡፡
  • ከምድር ዳርቻ ደመናውን ያወጣልመብረቅንም  በዝናም ጊዜ አደረገ ዝናምንም  እንደ መሽረብ ነጠብጣብ ያፈሳል ጉምን እንደ አመድ ይበትነዋል በረድንም  እያጠቃቀነ ያወርዳልለእንስሳም ሣሩን ያለመልማል፡፡
  • እንዳሰበ ያደርጋልእንደ ጀመረም  የጀመረውን ይፈጽማል እንደወደደም ያከናውናል፡፡ ያሳዝናል ደስ ያሰኛል ያደያል ባለጸጋም ያደርጋል፡፡ ያዋርዳል ያከብራል ይገድላል ያድናልም ድውይ ያደርጋል ይፈውሳልም  ይኮንናል ያጸድቃልም፡፡
  • የወደደውን ይምራልሊያስጨንቀው  የወደደውን ያስጨንቃልየሚምረውን  ይምረዋል፡፡ ይቅር የሚለውን ይቅር ይለዋል፡፡

No comments:

Post a Comment