Wednesday, April 20, 2016

ቅዳሴ ሠለስቱ ምእት (ክፍል ሁለት)


·         እግዚአብሔር አብ አንድ ልጁን የሰደደው ባል በማታውቅ በወለት ጋ ያድር ዘንድ ነው፡፡ ሕፃናትን የሚፈጥር እርሱ ሳይወሰን በማፀን ተወሰነ፡፡ አምላክ ሲሆን ሰው ሆነእሳተ መለኮትም ሲሆን ተወለደ አደገበጌጥና በክብር አይደለም፡፡ እንደ ድሆች ልጆች ለዘመዶቹ እየታዘዘ በብዙ ተግጽ አደገ እንጂ፡፡
·         ት ንጹ ሲሆን ባያ ያጠምቀው ዘንድ ራሱን አዘነበለ፡፡ ን ጠጅ እስከማድረግ ድረስ ተአምራትን አደረገ በምድረ በዳም ለብዙ ሰዎች እስኪያጠግብ ድረስ፡፡
·         ወዮ በዚያ ጊዜ የነበሩ ትውልድ እንዳያዩት አይናቸው ታወረ እንዳይሰሙት ጆቸው ደነቆረ እንዳያውቁትም ልቡናቸው ተሸፈነ፡፡ ኀትን ይቅር የሚለውን እሱን ዕሩቅ ብእሲን አስመሰሉት፡፡ በመንንት ላይ የሚፈርደውን ፈረዱበት፡፡
·         ከእነርሱም ወገን አስራ ሁለት ሐዋርያትን መረጠከእነርሱም ጋራ ተመላለሰ፡፡ የቁርባን ምጢረ ሥርትንም አሳያቸው፡፡
·         በዚያች ሌሊት ያዙት በነጋም ጊዜ የአይሁድ መምህሮችና የካህናት አለቆች ከገዥ ከላጦስ ጋራ ሊፈርዱበት በአደባባይ ተቀመጡ፡፡
·         እንደ ሌባ የሊት አሰሩት እንደ የዋህ በግ በፍቅር ተከተላቸው፡፡ ሊፈርዱበት በአደባባይ ተቀመጡ፡፡ የመላእክት ሰራዊት በመፍራት በመንቀጥቀጥ የሚቆሙለትን በፊታቸው አቆሙት፡፡
·         ክፉ ባርያ እርሱን ያልበደለውን ይጸፋው ዘንድ እጁን አጸና፡፡ የመላእክት አለቆች በፍጹም ድንጋፄ ለሚሰግዱለት ለእርሱ በትዕቢት ይሰግዱ ዘንድ አጎነበሱለት፡፡
·         የሕይወትን ራስ የሾህ ዘውድ ደፉበት፡፡ ብርሃንን እንደ ልብስ የሚጎናጸፈውን ልብሱን ገፈው ቀይ ግምጃ አለበሱት፡፡
·         ወደሚሰቅሉበት ስሙ ቀራንዮ ወደሚባል አገር ወሰዱት፡፡ መስቀሉን አሸከሙት ኢየሱስም መስቀሉን በመሸከም ደከመ ወዛ ከባድ ነውና፡፡ ንበዴዎች ጋራ ቆጠሩት፡፡ ወደ እንጨትም አውጥተው ምህረት የሌለው ስቅለትን እንደ ሕጋቸው ሰቀሉት፡፡
·         አዳምን የፈጠሩ እጆች ወዮ በመስቀል ቀኖት ተቸነከሩ፡፡ በገነት የተመላለሱ እግሮች ወዮ በመስቀል ቀኖት ተቸነከሩ ፡፡
·         በአዳም ፊት የሕይወትን መንፈስ እፍ ያለ አፍ ወዮ ከሐሞት ጋራ መጣጣንና ከርቤን ጠጣ፡፡
·         ኢየሱስ በሕማሙ (በመከራው ) አሰምቶ ጮኸ፤ ወደ አባቱ ጮኸ፡፡ ራሱን ዘለስ አደረገ ያን ጊዜ ነፍሱ ወጣች (ተለየች ) ፡፡
·         ርሱ ብለው ባሰሩት በጥቁር ጦር ጎኑን ወጉት፡፡ ከእንጨት አውርደው በመቃብር አኖሩት፡፡ ነርሱ መቃብር ያኖሩት አይደለም፡፡ ከከተማ ጭ ሶስት ክንድ በሚሆን በስደተኛ መቃብር ነው እንጂ በደንጊያም ገጠሙት፡፡
·         በዚያም ሳለ ወደ ባሪያው ወደ አዳም ወደ ልጆቹም ሁሉ ጮኸ፡፡
·         ዳግመኛም የትንኤውን ክብር ይገልጽ ዘንድ ጥቂት ብርሃኑን አወጣ መቃብሩን የሚጠብቁትንም ጣላቸው፡፡
·         በሦስተኛይቱ ቀን ተነሳ፡፡ በተረጋገጠች ቀን ደቀመዛሙርቱ ወዳሉበት ገብቶ የጎኑን መወጋት የእጆቹን መቸንከር አሳያቸው፡፡ የመንግሥተ ሰማያትን ነገር እያስተማራቸው ከነርሱ ጋር ኖረ፡፡
·         በዐርባኛውም ቀን ወደ ላከው አብ ወደ ሰማይ ዐረገ፡፡ ዳግመኛም ይመጣል በትህትና የሚመጣ አይደለም በወለደው በአብ ጌትነት በሚያስፈራ ስልጣን ከቅዱሳን መላእክቶቹ ጋራ በሰማይ ደመና ነው እንጂ፡፡
·         አቤቱ ሞትህን ቅድስት ትንሣኤህንም እንናገራለን፡፡ እርገትህን ዳመኛም መምጣትህን እናምናለንእናመሰግንሃለን እናምንሃለን፡፡ ጌታችንና አምላካችን ሆይ እንለምንሃለን እንማልድሃለንም፡፡
·         አቤቱ ይቅርታህ ለኛ ትደረግልን፡፡ በአንተ እንዳመንን መጠን፡፡
·         መሰብሰቢያችንም እንደ ደቀ መዛሙርትህ መሰብሰብ ይሁን፡፡ ነርሱ ፈጣሪ አንተ ነህ፡፡ ኛም አንተ ነህ፡፡ያንጊዜ የነበርህ አንተ ነህዛሬም ያለህ አንተ ነህ፡፡
·         ሰማያት ያንተ ናቸው ምድርም ያንተ ናት፡፡ ጻድቃን ያንተ ናቸው ኃጥአንም ያንተ ናቸው፡፡ ብዙውን ኀጢአት ይቅር ትላለህና፡፡ ጥቂቱን ስለ ጽድቅ ታቆማለህ፡፡ ለመዳንም ምክንያት ትሻለህ፡፡
·         ከርሱ ለሚቀበሉ ሁሉ አንድ አድርገህ ስጣቸው፡፡ ለሚቀበሉት ንጽሕን ይሆናቸው ዘንድ፡፡ ለሚቀበሉትም መመረጫ ይሆናቸው ዘንድ፡፡ እርሱን በማየት የኀጢአት እሾህነት ይቃጠል ዘንድአበሳ ትነቀል በደልም ትጠፋ ዘንድነፍስም ከበደልዋ ፈጽማ ታርፍ ዘንድ፡፡
·         የብርሃን ደጅ ይገለጥ፡፡ የብርሃን በርም ይከፈት፡፡ ቅዱስና ሕያው የሚሆን መንፈስም ይላክ፡፡ አኗኗሩ ከተሰወረ ቦታ ይውረድ ምጣም፡፡
·         ከሁሉ በላይ የምትሆን የአንዲት ቅድስት ቤተክርስቲያን የማህበሯን ፍጻሜ ማራቸው፡፡ ይቅርም በላቸው፡፡ይልቁንም ይህንን ምስጢር ለማገልገል የኔን ንዴት የመረጡትን ማራቸው፡፡ ይቅርም በላቸው፡፡ ለዘለዓለሙ አሜን፡፡
·         የአንተ በሚሆን በመንፈስ ቅዱስ አንድ እንሆን ዘንድ መሆንን ስጠን፡፡ በዚህም ጵርስፎራ (በስጋው በደሙ) አድነን፡፡ ለዓለሙ ሁሉ በምትሆን በአንተ ለዘለዓለሙ ሕያዋን እንሆን ዘንድ፡፡
·         የእግዚአብሔር ስም ምስጉን ነው በእግዚአብሔር ስም የሚመጣውም ምስጉን ነው፡፡ የጌትነቱም ስም ይመስገን ይሁን ይሁን የተመሰገነ ይሁን፡፡
·         ዳግመኛም ዓለምን የያዘውን ከታቸውም ቤዛ የሆናቸውን እርሱን እንማልደዋለን፡፡ ከቅድስት ድንግል የነሳጋ የጋ እንደሆነ ከሰማይ ያወረድከው እንዳይደለ አስብ፡፡
·         ከቅድስት ድንግል የነሳጋ የማሪያ መዘጋትን የተሸከመ ጋ እንደሆነ አስብ፡፡
·         ከቅድስት ድንግል የነሳጋ የታመመው የሞተውም እንደሆነ አስብ፡፡
·         ከቅድስት ድንግል የነሳጋ በሶስተኛው ቀን ከሙታን ተለይቶ የተነሳው ጋ እንደሆነ አስብ፡፡
·         ከቅድስት ድንግል የነሳጋ በክብር በምስጋና ወደ ሰማይ ያረገ በአባቱም ቀኝ የተቀመጠው እንደሆነ አስብ፡፡ዳግመኛም አምላካችን እግዚአብሔር በዚህ ጋ ከመለኮቱ ይል ጋራ ይመጣል፡፡
·         ነፍሳችሁን መርምሩ ሰውነታችሁንም አንጹ፡፡ ኛ ወገን ማንም በበደልና በት ብዛት አይታመም፡፡
·         የእግዚአብሔር በግ አማኑል እነሆ ዛሬ ከኛ ጋራ በዚህ ዕድ ላይ አለ፡፡ እነሆ ብርሃን አብ ከልጁ ጋራ ከመንፈስ ቅዱስም ጋራ አለ፡፡
·         ቤተክርስቲያንን የሚጎበኙ የብርሃን መላእክት እነሆ አሉ፡፡ ነፍሳችሁን መርምሩ ሰውነታችሁንም አንጹ፡፡ ኛ ወገን ማንም ማን አይታመም፡፡ የበደል አለ ትም አለይህንንም ምስጢር ለመቀበል የተገባን እንሆን ዘንድ ሊናችንን ንቁሕ እናድርግ ለዘለዓለሙ፡፡
·         በልጅህ በወዳጅህ በኢየሱስ ክርስቶስ ወደ ጌትነትህ ገናንነት ፊት ያቀረብከን አቤቱ እናመሰግንሃለን ለአንተ ጌትነትና ክብር ምስጋናም ይገባል ለዘለዓለሙ አሜን፡፡
·         ያ ቃል ቀድሞ የነበረ ነው፡፡ ያ ቃል የእግዚአብሔር ቃል ነው፡፡ ያ ቃል ጋ ሆነ በኛም አደረ፡፡  ለአባቱ እንደ አንድ ልጅ ክብር የሚሆን ክብሩን አየን፡፡ ያ ቃል ወደ ወገኖቹ መጣ ወገኖቹ ግን አልተቀበሉትም፡፡
·         የተቀበልነው እኛ ሶስት መቶ አስራ ስምንቱ ነን፡፡ ሃይማኖትን ያቀናን ሙሽራዋ አምላካችን እግዚአብሔር የሆነ የቅድስት ቤተክርስቲያንን ሕግ የሰራን፡፡
·         አይኖቻቸው ብዙዎች የሚሆኑ ኪሩቤልክንፎቻቸው ስድስት የሚሆኑ ሱራፌል የሚከቡህ አንተ ነህ፡፡
·         አዳምን በአንተ አርአያና አምሳል የፈጠርከው ሆይ እሳትን በው ላይ ያሰፈርከው ሆይ ጨለማ የማይጨልምበት ሌሊትም የማይሰወረው ሆይ ወደዚህ ምስጢር ፊት ያቀረብከን አንተ ነህ፡፡ ለአንተ ጌትነት ክብር ምስጋናም ይገባል ለዘለዓለሙ፡፡
·         አቤቱ አምላካችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ ባርከን ቀድሰን፡፡ ያለ ት ያለ ርኩሰት በፍጹም ደስታ ወደ ቤታችን ለመሄድ የበቃን እንድንሆን አድርገን፡፡
·         ከክብርት ማዕድ የተቀበልነው ጋህና ደምህ የሚያድነን ይሁንልን፡፡
·         አቤቱ ቅዱስ መንፈስንም ላክልን ወደ ጽድቅና ወደ ሕይወት ጎዳና ይመራን ዘንድ፡፡
·         የሕያው እግዚአብሔር ልጅ ሥጋውንና ደሙን በዚህ ዓለም ሰራ፡፡ ርሱ በልተን ከርሱ ጋር እንኖር ዘንድ፡፡
·         ሕያውና ቅዱስ በሚሆን መሰዊያህ ዘንድ በምሕረትህ ወደ አንተ አቅርበን የእግዚአብሔር ባሮች የልዑልም ማረፊያ (ማደሪያ )እንባል ዘንድ፡፡ ሁላችንም ወደርሱ እንቅረብ በልመናና በስግደት በጸሎትና በንጽህና በማመን ከፊቱ እንደርስ ዘንድ፡፡
·         በየጊዜው ሁሉ በየሰዓቱም ሁሉ ጸሎትንና ልመናን በሚያሳርጉ በካህናት እጅ የተቀበልነው ቅዱስ ሥጋውና ክቡር ደሙ ለሕይወት ለተስፋ ለመድኃኒትና ለት ማስተስ ከሙታንም ተለይቶ ለመነሳት ይሁነን ለዘለዓለሙ አሜን፡፡















    








                           

No comments:

Post a Comment